ዛሬ፡መስከረም18: ቀን (28 Sept 2018)
✞ በዓለ መስቀልን ምክንያት በማድረግ ከብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ ✞ በመጀመሪያ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ፥ አደረሰን! ለዛሬ ንዑድ ክቡር ከሚኾን ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር ያደረግሁትን [ምናባዊ] ቃለ መጠይቅ እጋብዛችኋለሁ፤ መልካም ቆይታ! #ጥያቄ፡- አባታችን በመጀመሪያ በዓሉን ምክንያት በማድረግ ለልጆችህ ምዕዳን ለመስጠትና ለምንጠይቅህ አንዳንድ ጥያቄዎች መልስ ትሰጠን ዘንድ ፈቃድህ...