ዛሬ፡ጳጉሜን3፡ቀን (Sept 8 2018)

*እንኳን፡ለሊቀ፡መላእክት፡ለቅዱስ፡­ሩፋኤል፡ለተሾመበት፣ጦቢትን፡አይኑን፡ለአበራለትና፡ል­ጁ፡ጦብያን፡ለረዳበት፣የራጉኤልን፡ልጅ፡ሣራን፡ተቆራኝቷት፡ከነበረው፡ከአስማንድዮስ፡ጋኔን፡ለአዳነበት፡በዓል፣ለሊ­ቀ፡ካህን፡ለኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ምሳ­ሌ፡ለሆነ፡ለካህኑ፡መልከፄዴቅ፡ለመታ­ሰቢያ፡በዓሉና፡ለኢትዮጵያ፡ንጉስ፡መል­ካም፡ስም፡አጠራር፡ላለው፡ለአፄ፡ዘር­ዐ፡ያዕቆብ፡ለዕረፍቱ፡ቀን፡መታሰቢያ­፡በሰላም፡አደረሰን።በተጨማሪ፡በዚች፡ቀን፡በስንክሳሩ፡ከሚታሰበው፦ሰንዱን፡ከሚባል፡አገር፡ከቅዱስ፡ሰራጵዮን፡ዕረፍት፡ረድኤትና፡በረከትን፡ያሳትፈን፡። “ሰላም፡ለአፃ­ብኢከ፡አዕይንተ፡ጦቢት፡ዘፈሳ።ወለ­አፅሪከ፡ደርገ፡ዘኵሕላ፡ሐሞት፡ዓሣ­።መልአከ፡ምሥጢር፡ሩፋኤል፡ወዘውገ­፡ርቡዓን፡እንስሳ።አዕይንትየ፡እግ­ዚኦ፡አፃአብከ፡ይግሥሣ።ከመ፡እደ፡­መልአክ፡ገስሳ፡ለነቢይ፡ዘሱሳ።”ት­ርጉም፦ቅዱስ፡ሩፋኤል፡ሆይ፡የጦቢትን፡ዐይ­ኖች፡ለወሱ፡ጣቶችህ፡ሰላም፡እላለሁ­።ለመፈወሱ፡በመተባበር፡የዓሣ፡ሐሞ­ትን፡ለኳሉ፡ጥፍሮችህም፡ሰላም፡እላ­ለሁ።ሩፋኤል፡ሆይ፡የኪሩቤል፡ወገን­፡የምትሆን፡መለኮዊ፡ምሥጢርን፡የም­ትነግር፡ነህና።የሕይወት፡መልአክ፡­እጅ፡የሱሳን፡ነቢይ፡እንደ፡ዳሰሰ።­አቤቱ፡ጣቶችህ፡ዓይኖቼን፡ይዳስሱል­ኝ።መልክአ፡ቅዱስ፡ሩፋኤል። *”ሰላም፡ለሩፋኤል፡መልአከ፡ነፍስ”።ትርጉም፦የነፍስ(የሰውነት)መልአክ፡ለኾነ፡ለቅዱስ፡ሩፋኤል፡ሰላምታ፡ይገባል”። *”ሰላም፡ለመልከ፡ጼዴቅ፡ዐቢይ፡ካህን፡አምሳሊሁ፡ለወልደ፡እግዚአብሔር፤ዘእእመረ፡ምስጢሮ፡ኅቡአ፡ዘሀሎ፡ይትገበር”።ትርጉም፦ሊከናወን(ሊፈጸም)ዘንድ፡ያለውን፡ስዉር(ድብቅ)ምስጢሩን፡ያወቀ፤ለእግዚአብሔር፡ልጅ፡ምሳሌው፡ለኾነ፡ለታላቁ፡ካህን፡ለመልከ፡ጼድቅ፡ሰላም፡ይገባል።አባ፡ጊዮርጊስ፡ዘጋስጫ፡በተአምኆ፡ቅዱሳን፡ላይ። *የዕለቱ፡ዓራራይ፡ዜማ፦”ይቤሎ፡ለጦብያ፡አነ፡ውእቱ፡ሩፋኤል፡መልአክ፡አሐዱ፡እምሰብዓቱ(ተሰዓቱ)ሊቃ፡መላእክት፡ዘተፈኖኩ፡ኀበ፡ጦቢት”።ትርጉም፦ለጦብያ፡ከሰባቱ(ዘጠኙ)ሊቃነ፡መላእክት፡አንዱ፡ወደ፡ጠቢት፡የተላኩኝ፡ሩፋኤል፡መልአክ፡እኔ፡ነኝ፡አለው ። *የዕለቱ፡ምልጣን፡ግዕዝ፡ዜማ፦”ይሰግዱ፡በብረኪሆሙ፡ወያሌዕሉ፡ህሊናሆሙ፡በጥንቃቄ፡ወበኅሢሥ፡ኀበ፡እግዚኦሙ፡ንጉሥ፡ቀዋምያን፡ለነፍሳት፡እሙንቱ፡ሊቃናት፡ዑራኤል፡ወሩፋኤል፡ይትፌነው፡ለሣህል፡እምኀበ፡ልዑል”፡፡ትርጉም፦ወደ፡ጌታቸው፡ንጉሳቸው፡ይሰግዳሉ፡ህሊናቸውንም፡በጥንቃቄ ከፍ፡ከፍ፡ያደርጋሉ፡ለነፍሳት፡የሚቆሙ፡እነዚህ፡አለቆች፡ዑራኤልና፡ሩፋኤል፡ከልዑል፡ለይቅርታ፡ይላካሉ፡፡ቅዱስ፡ያሬድ፡በድጓው፡ላይ። *የዕለቱ­፡ምስባክ፦”እግዚአብሔር፡ገሃደ፡ይ­መጽእ።ወአምላክነሂ፡ኢያረምም።እሳ­ት፡ይነድድ፡ቅድሜሁ።“መዝ49፥2-­3።የሚነበው፡ወንጌል፡ማቴ25፥31­-46።የሚቀደሰው፡ቅዳሴ፡የቅዱስ፡ያዕቆብ­፡ዘሥሩግ፡ነው።­መልካም፡በዓል፡ለሁላችን፡ይሁንልን­።

Continue reading