መስከረም17፡ቀን (27 Sept 2018)

*”በስመ፡አብ፡ወወልድ፡ወመንፈስ፡ቅዱስ፡አሐዱ፡አምላክ፡አሜን”።
        *መስከረም17፡ቀን
*እንኳን፡ለጌታችን፡ለአምላካችን፡ለ­መድኃኒታችን፡ለኢየሱስ፡ክርስቶስ፡­የመስቀል፡በዓል(የጻድቁ፡ንጉሥ፡የቆስጠንጢኖስ፡እናት፡ንግሥት፡ቅድስት፡ዕሌኒ፡ከተሠወረበት፡በደመራ፡ጢስ፡ቦታው፡ከተገለጠላት፡በኋላ፡ቁፍሮ፡ያስጀመረችበት፡ነው)በሰላም፡አደረሰን­።በተጨማሪ፡በዚች፡ቀን፡ከሚታሰቡ፡­የከበረች፡ሮማዊት፡ታኦግንስጣና፡ከ­ሊቀጳጳስ፡ከአባ፡ዲዮናስዮስ፡ከዕረፍታቸው፡በዓል፣ከሊቢባ፣ከኪርያኖስ፣ከዮስጢናና፡ከቴክሴልጥስ፡ከመታሰቢያቸው፡ረድ­ኤትና፡በረከትት፡ያሳትፈን።
*”ሚመጠነ፡ሀብተ፡ጸጋ፡ተውህለ፡ለክብር፡ዕፀ፡መስቀል።መስቀልከ፡ንዋየ፡ሐቅል፡ለፀብእ፡ወሰይፈ፡መለኮት፡ዘሐራ፡ዚአከ።መስቀልከ፡ገፍታኤ፡ማዕከል፡እንተ፡ጽልእ፡ወነሳቴ፡ጥቅም፡ዘኃጣውእ።መስቀልከ፡አብ፡ለእጓለ፡ማውታ፡ወመኰንኖሙ፡ለዕቤራት።መስቀል፡መርስ፡ለእለ፡ይትመነደቡ፡በባሕር፤ወመርሶ፡ለእለ፡ይሳኵዩ፡ውስተ፡በደው።መስቀል፡መርሐ፡ዕውር፡ወምርጉዘ፡ሐንካሳን፡ወኃይሎሙ፡ለፅቡሳን።መስቀልከ፡ዕፅ፡ዘያልሕቅ፡ሕፃናተ፡መሃይማናን፡በአጥባተ፡ቅድስት፡ቤተ፡ክርስቲያን።መስቀልከ፡አክሊለ፡ነገሥታት።መስቀልከ፡ትምክህቶሙ፡ለመሲሐውያን።መስቀልከ፡ዘይሴርዎሙ፡ለመሠርያን፡ወይዘርዎሙ፡ለመሰግላን።መስቀልከ፡ሰያሚሆሙ፡ለካህናት፡ወአሳዬ፡ሩጸቶሙ፡ለዲያቆናት።መስቀልከ፡ዘያነሥኦሙ፡ለውዱቃን፤ወያረውጾሙ፡ከመ፡ኀየል፡ለፅውሳን።መስቀልከ፡ዘኮነ፡ሕፄሃ፡ለመርዓት፡ወሕዳጋቲሃ፡ለእንተ፡ደኃርካ፡በምኵራብ።መስቀልከ፡መሠረተ፡አሚን፡ወዓምደ፡ሃይማኖት፡ለእለ፡ይትዌከሉ፡ቦቱ።መስቀልከ፡መብጠሌ፡ኵሉ፡ስራይ፡ወመፅርዔ፡ኵሉ፡ሰገል።በመስቀልከ፡ወበሰይፈ፡መዓትከ፡ሠርዎሙ፡ለፀረ፡መስቀልከ።ወእለ፡ይፈቅዱ፡ይገፍትኡ፡ወንጌለ፡መለኮትከ፡ይኩነ፡ግፍቱዓነ፡እምገጸ፡ምድር”።ትርጉም፦ለክቡር፡መስቀል፡የተሰጠው፡የጸጋ፡ሀብት፡እንደምን፡የሚያህል፡ነው!መስቀልህ፡በውጊያ፡ጊዜ፡የጦር፡መሣርያ፣ለወታደሮችህም፡የመለኮት፡ሰይፍ፡ነው፤መስቀልህ፡በጠብ፡ጊዜ፡ማዕከሉን፡የሚመታ፣ኃጢአትንም፡ግንብ፡የሚያፈርስ፡ነው፤መስቀል፡ለሙት፡ልጆች፡አባት፡ለባልቴቶችም፡ዳኛ፡ነው፤መስቀልህ፡በባሕር፡ለሚጨነቁ፡ጸጥ፡የሚያደርግ፣በምድረ፡በዳ፡ለሚከራተቱም፡ወደብ፡ነው፤መስቀልህ፡ለዕውራን፡መሪ፤ለአንካሶችም፡ምርኩዝ፣ለድኩማንም፡ኃይላቸው፡ነው፤መስቀልህ፡ሕፃናት፡ምእመናንን፡በቤተ፡ክረስቲያን፡ጡቶች፡የሚያሳድግ፡ዕፅ፡ነው፤መስቀልህ፡ለነገሥታት፡አክሊል፡ነው፤መስቀልህ፡ለክርስቶሳውያን፡ትምክህታቸው፡ነው፤መስቀልህ፡ጠንቋዮችን፡የሚያጠፋ፣እናውቃለን፡ባዮችንም፡የሚበትን፡ነው፤መስቀልህ፡የካህናት፡ሰያሚያቸው፣የዲያቆናትም፡የተልዕኳቸው፡ሽልማት፡ነው፤መስቀልህ፡የወደቁትን፡የሚያነሣቸው፣ደካሞችንም፡እንደ፡ዋልያ፡የሚያሮጣቸው፡ነው፤መስቀልህ፡ለሙሽራህ፡ለቤተ፡ክርስቲያን፡ጥሎሿ፣በምኩራብ፡ለፈታሃትም፡ምልክቷ፡ነው፤መስቀልህ፡በእርሱ፡ለሚታመኑ፡የእምነት፡መሠረት፣የሃይማኖትም፡ዓምድ፡ነው፤መስቀልህ፡ጥንቆላን፡ሁሉ፡ማርከሻ፣መተትንም፡ሁሉ፡ማጥፊያ፡ነው፤በመስቀልህና፡በቁጣህ፡ሰይፍ፡የመስቀልህን፡ጠላቶች፡በትናቸው፤የመለኮትህንም፡ወንጌል፡ሊያጠፋ፡የሚፈልጉ፡ሁሉ፡ከምድር፡ገጽ፡የጠፋ፡ይሁኑ።አባ፡ጊ­ዮርጊስ፡ዘጋሥጫ፡በውዳሴ፡መስቀል፡­ላይ4፥61።
*የዕለቱ፡ምልጣን፡ግእዝ፦”ይቤሎሙ፡ኢየሱስ፡ለአይሁድ፡እመኑ፡ብየ፡ወእመኑ፡በአቡየ፡ዮምሰ፡ለእሊዓየ፡አበርህ፡በመስቀልየ”።ትርጉም፦ኢየሱስ፡አይሁድን፡በእኔ፡እመኑ፡በአባቴም፡እመኑ፡ዛሬ፡ለወዳጆቼ፡በመስቀሌ፡አበራለሁ፡፡
*የዕለቱ፡ዓራራይ፡ዜና፦”መስቀል፡ብርሃን፡ለኲሉ፡ዓለም፡መሠረተ፡ቤተክርስቲያን፡በከመ፡ይቤ፡ዳዊት፡በመዝሙር፡ሐነጸ፡መቅደሶ፡በአርያም”።ትርጉም፦መስቀል፡ብርሃን፡ነው፤ለዓለም፡ሁሉ፡የቤተክርስቲያን፡መሰረነው።ዳዊት፡በመዝሙር፡በአርያም፡ማደሪያውን፡ስራ፡እንዳለ፡፡ቅዱስ፡ያሬድ፡በድጓው፡ላይ።
*የዕለቱ፡ምስባክ፦”ወረከብናሁ፡ውስተ፡ኦመ፡ገዳም።ንበውዕ፡እንከሰ፡ውስተ፡አብያቲሁ፡ለእግዚአብሔር።ወንሰግድ፡ውስተ፡መካን፡ኀበ፡ቆመ፡እግረ፡እግዚእነ።”መዝ131፥6-7፡ወይ­ም፡መዝ59፥4-5፡።የሚነበው፡ወ­ንጌል፡ዮሐ19፥25-28ወይም፡ማቴ­8፥16-28።የሚቀደሰው፡ቅዳሴ፡የቅዱስ፡­ዮሐንስ፡አፈወርቅ፡ቅዳሴ፡ነው።መል­ካም፡በዓል፡ለሁላችንም፡ይሁንልን።

Comments are closed.