ዛሬ፡ጳጉሜን4፡ቀን

*እንኳን፡ለታላቁ፡ለተጋዳይ፡አባት፡ለአባ፡ባይሞንና፡ለሮሜ፡ሊቀ፡ጳጳሳት፡ሊባርዮስ፡ለዕረፍታቸው፡በዓል፡በሰላም፡አደረሰን።በተጨማሪ፡በዚች፡ቀን፡በስንክሳሩ፡ከሚታቡ፦ከአባ፡ባይሞን፡ከስድስቱ፡ወንዱሞቹ፡መነኰሳት፡ሰማቸው፡ከዮሐንስ፣ከኢዮብ፣ከዮሴፍ፣ከላስልዮስ፣ከያዕቆብና፡አብርሃም፡ከመታሰቢያቸው፡ረድኤትና፡በረከትን፡ያሳትፈን።
*”ሰላም፡ዕብል፡በልሳንየ፡መዋቲ።፯ተ፡አኃወ፡ኅዱራነ፡በአት፡አሐቲ።ሶበ፡ፈቀደት፡እሞሙ፡ትርእዮሙ፡ይቤልዋ፡ላቲ።ኢትክሊ፡ትርአዪነ፡በዓለም፡ሰማይ፡እንታክቲ።ለእመ፡በዝየ፡ርኢክነ፡አንቲ”።አርከ፡ሥሉስ፡(አርኬ)የጳጉሜን4።
*የዕለቱ፡ዓራራይ፡ዜማ፦”ማዕረሩሰ፡ኀልቀተ፡ዓለም፡ውእቱ፡ወአፀዱኒ፡እሙንቱ፡መላእክት፡እምበለስ፡አእምሩ፡አምሳሊሁ፡እምከመ፡በጽሐ፡ጊዜሁ፡ይፌንዎሙ፡ለመላእክት፡በቃለ፡ቀርን”።
ትርጉም፡- መከሩስ(ማ)የዓለም፡ፍጻሜ፡ነው፡አፃጆችም፡መላእክት፡ናቸው፡ምሳሌውን፡ከበለስ፡እወቁ(ተማሩ)ጊዜው፡በደረሰ፡ጊዜ፡መላእክትን፡በመለከት፡ቃል፡ይልካቸዋል፡፡
*መዝሙር፡ዘሰንበት(የዚህ፡ሳምንት፡መዝሙር)፦”ከመ፡እንተ፡መብረቅ፡ዘይወጽእ፡እምጽባሕ።ወያስተርኢ፡እስከ፡ዓረብ።ከማሁ፡ምጽአቱ፡ለወልደ፡እግዚአብሔር።ምስለ፡ኃይለ ሰማያት፡በንጥረ፡መባርቅት።ከመ፡እንተ፡መብረቅ፡ዘይወጽእ፡እምጽባሕ።ምስለ፡አእላፍ፡መላእክት፡ወኲሎሙ፡ሊቃነ፡መላእክት።ከመ፡እንተ፡መብረቅ፡ዘይወጽእ፡እምጽባሕ።አክሊለ፡አክሊላት፡ዲበ፡ርእሶሙ፡ለካህናት”።ቅዱስ፡ያሬድ፡በድጓው፡ላይ።
*የዕለቱ­፡ምስባክ፦”እግዚአብሔር፡ገሃደ፡ይ­መጽእ።ወአምላክነሂ፡ኢያረምም።እሳ­ት፡ይነድድ፡ቅድሜሁ”።መዝ49፥2-­3።የሚነበው፡ወንጌል፡ማቴ17፥11­-37።የሚቀደሰው፡ቅዳሴ፡የቅዱስ፡ያዕቆብ­፡ዘሥሩግ፡ነው።­መልካም፡በዓል፡ለሁላችን፡ይሁንልን­