ዛሬ፡መስከረም2፡ቀን (Sept 12 2018)

*እንኳን፡ለታላቁ፡ነብይ፣ሰማዕት፣ሐ­ዋርያ፣ካህን፡ለመጥምቀ፡መለኮት፡ቅ­ዱስ፡ዮሐንስ፡ሕግ፡አፍራሽ፡በሆነ፡­በንጉስ፡ሄሮድስ፡እጅ፡አንገቱን፡በ­መሰየፍ፡ሰማዕትነት፡ለተቀበለበት፡­በዓል፡በሰላም፡አደረሰን።በዚች፡ቀ­ን፡በጨማሪ፡በስንክሳሩ፡ከሚታሰቡ፦በግብጽ፡ውስጥ፡ታዕዳ፡ከሚባል፡አገር፡በሰማዕትነት፡ከዐረፈ፡ከቅዱስ፡ዳስያ፣ከሰ­ማዕት፡ዲዲሞስና፡ቅድስት፡መሪና፡ከመታሰቢያቸው፡ረድኤትና፡በ­ረከትን፡ያሳትፈን።
*”ሰላም፡ለዮሐንስ፡ግፋዕ፡ወቅቱል፡ንጹሕ፡ወቅዱስ፡ወስቡሕ፡ላእክ፡ወነቢይ፡ወሰማዕት፡ድንግል፡ካህን፡ጸያሒ፡ወሰባኪ፡መጥምቀ፡እግዚኡ”።ትርጉም፦ጌታውን፡ያጠመቀና፡ሰባኪ፤መንገድ፡ጠራጊ፣ካህን፡ድንግል፡ሰማዕት፣ነቢይና፡አገልጋይ፤ምስጉን፡ቅዱስና፡ንጹሕ፤ተገፍቶ፡የተገደለ፡ለኾነ፡ለቅዱስ፡ዮሐንስ፡ሰላምታ፡ይገባል።አባ፡ጊዮርጊስ፡ዘጋስጫ፡በተአምኆ፡ቅዱሳን፡ላይ።
*የዕለቱ፡ምልጣን፡ግእዝ፡ዜማ፦ሃሌ፡ሉያ­”እምኄሶ፡ለሄሮድስ፡ይብላዕ፡መሐላ­ሁ፡እምያምትር፡ርዕሶ፡ለዮሐንስ፡ዐ­ቢይ፡ነቢይ፡ሰባኬ፡ጥምቀት፡ለንስሐ፡ከመ፡ይመኑ፡ህዝብ፡በብርሃኑ።”ትርጉ­ም፦ሄሮድስ፡ከፍ፡ያለ፡ነቢይ፡ህዝቡ፡በብርሃኑ(በጌታች፡በአምላካች፡በመድኃኒታችን፡በኢየሱስ፡ክርስቶስ)፡ያምኑ፡ዘንድ፡ለንስሐ፡የሚሆን፡ጥምቀ­ትን፡የሚሰብክ፡የዮሐንስን፡ራስ፡ከ­ሚቆርጥ፡መሐላውን፡ቢበላ፡በተሻለው­፡ነበር።ቅዱስ፡ያሬድ፡በድጓው፡ላይ።
*የዕለቱ፡ምስባክ፦”ወይርአ­ዩ፡አሕዛብ፡በቅድመ፡አዕይንቲነ።በ­ቀለ፡ደሞሙ፡ለአግብርቲከ፡ዘተክዕወ­።ይባዕ፡ቅድሜከ፡ገዐሮሙ፡ለሙቁሓን”።መዝ78፥10-11።የሚነበበው፡­ወንጌል፡ማርቆስ6፥14-30።የሚቀ­ደሰው፡ቅዳሴ፡የዮሐንስ፡ወልደ፡ነጎ­ድጓድ፡ቅዳሴ፡ነው።መልካም፡በዓል፡­ለሁላችንም፡ይሁንልን።